31 ጥቅምት 2023

አርጀንቲናዊው የኢንተር ማያሚ አጥቂ ሊዮኔል ሜሲ ለስምንተኛ ጊዜ የወንዶች ባለን ኦር አሸናፊ ሆነ።የ36 ዓመቱ ሜሲ ባለፈው ዓመት በተካሄደው የኳታር ዓለም ዋንጫ ሃገሩን ለክብር በማብቃቱ ነው ፓሪስ በተካሄደው ሥነሥርዓት እውቅና ያገኘው። እንግሊዛዊው የሪያል ማድሪድ አማካይ ጁድ ቤሊንግሃም 21 ዓመት በታች ለሆኑ ተጫዋቾች የሚሰጠውን ኮፓ ዋንጫ አንስቷል። ሊዮኔል ሜሲ ክብረ ወሰኑን ያራዘመበትን ባለን ኦር ያነሳው የማንቸስተር ሲቲውን ኧርሊንግ ሃላንድን በማስከተል ነው። በዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ሃትትሪክ በመሥራት በታሪክ ሁለተኛው ተጫዋች የሆነው ፈረንሳዊው ኪሊያን ምባፔ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።ለአንድ ተጨማሪ ጊዜ እዚህ መገኘት እና ይህን ታሪክ ማጣጣም ደስ የሚያሰኝያለው ሜሲ፤የዓለም ዋንጫን ማንሳቴ እና ሕልሜን ማሳካቴ ደስተኛ አድርጎኛልሲል አክሏል። የቀድሞው የባርሴሎና እና የፓሪ ሳን ዠርማ የፊት መስመር ተጫዋች ጨምሮ ሁሉም የባለን ኦር ሽልማቶች ልዩ ቦታ እንዳላቸው ተናግሯል።

ማንቸስተር ሲቲ ታሪክ በፃፈበት ባለፈው የውድድር ዘመን የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ፣ ቻምፒዮንስ ሊግ እና የኤፍ ዋንጫ ያነሳው፤ 35 የሊግ ጨዋታዎች 36 ጎሎች ያስቆጠረው፤ በሁሉም ውድድሮች 52 ኳሶች ከመረብ ያገናኘው ሃላንድ ሜሲን በመከተል ሁለተኛ ሆኗል።ሃላንድ ለምርጥ ጎል አግቢዎች የሚሰጠውን የገርድ ሙለር ሽልማት ማንሳት ችሏል። ባለን ኦር የዓመቱን ምርጥ እግር ኳስ ተጫዋች የሚመርጥ ሲሆን ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ 100 ጋዜጠኞች ናቸው ድምፅ የሚሰጡበት።

አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ እንድታነሳ ያገዘው ሜሲ ክለቡ ኢንተር ማያሚ ሊግስ ካፕ የተሰኘውን ዋንጫ እንዲያነሳም ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። ሜጀር ሊግ ሶከር የተባለውን የአሜሪካ ሊግ የተቀላቀለው ሜሲ 14 ጨዋታዎች 11 ጎሎች አስቆጥሯል። ከሜሲ ቀጥሎ በርካታ ባለን ኦር ያነሳው ፖርቹጋላዊው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሲሆን አምስት ጊዜ ሽልማቱን ተቀብሏል። ለሳዑዲ አረቢያው አል ናስር የሚጫዋተው ሮናልዶ ከፈረንጆ 2003 ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የሽልማቱ ዕጩ ሳይሆን ቀርቷል። አርጀንቲናዊው ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ የዓመቱ ምርጥ ግብ ጠባቂ ተብሎ ያሺን ትሮፊ የተሰኘውን ሽልማት አግኝቷል።

የእንግሊዙ ክለብ ማንቸስተር ሲቲ የዓመቱ ምርጥ ክለብ የተባለ ሲሆን የፔፕ ጉዋርዲዮላ ቡድን ባለፈው ዓመት ሶስት አብይ ዋንጫዎችን በማንሳት በእንግሊዝ ታሪክ ሁለተኛው ቡድን መሆኑ ይታወሳል። የሪያል ማድሪዱ ብራዚላዊ የክንፍ ተጫዋች ቪኒሲየስ ጁኒየር ዘረኝነትን ከእግር ኳስ ለማስወገድ በሠራው ሥራ የሶክራቲስ ሽልማት ተበርክቶለታል።

የባለን ኦር ሽልማት ምርጥ 10

1. ሊዮኔል ሜሲ [አርጀንቲና / ፒኤስጂ / ኢንተር ማያሚ]

2. ኧርሊንግ ሃላንድ [ኖርዌይ / ማንቸስተር ሲቲ]

3. ኪሊያን ምባፔ [ፈረንሳይ / ፒኤስጂ]

4. ኬቪን ብሩይነ [ቤልጂየም / ማንቸስተር ሲቲ]

5. ርድሪ [ስፔን / ማንቸስተር ሲቲ]

6. ቪኒሲየስ ጁኒየር [ብራዚል / ሪያል ማድሪድ]

7. ጁሊያን አልቫሬዝ [አርጀንቲና / ማንቸስተር ሲቲ]

8. ቪክተር ኦሲምሄን [ናይጄሪያ / ናፖሊ]

9. በርናንዶ ሲልቫ [ፖርቹጋል / ማንቸስተር ሲቲ]

10. ሉካ ሞድሪች [ክሮኤሺያ / ሪያል ማድሪድ]

ኢትዮ ካብ ስለሚሰጠው አገልግሎት ለማወቅ ድህረገጻችንን www.ethiocab.com ይጎብኙ

Driver application ለማውረድ http://driver.ethiocab.com እንዲሁም Customer application ለማውረድ  http://user.ethiocab.com     

አብረን ሰርተን ትርፋችንን እንካፈል  !!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *